በ3ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ኘሪምየር ሊግ ጨዋታ ወላይታ ሶዶ ላይ ወላይታ ዲቻን ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ ያገናኘው ጨዋታ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት የሚጀመር ሲሆን ካፍ ኢንስትራክተር መኮንን አስረስ የጫወታው ታዛቢ (ኮሚሽነር) ሆነው ሲመሩ በዋና ዳኝነት ፌድራል ዳኛ አዳነ ወርቁ፣ 1ኛ ረዳት ኢንተርናሽናል ሸዋንግዛው ተባባል፣ 2ኛ ረዳት ዳኛ ፌደራል ዳኛ ይበቃል ደስአለኝ ሲሆኑ ኢንተርናሽናል ቴዎድሮስ ምትኩ አራተኛ ዳኛ በመሆን ጨዋታውን ይመሩታል።፨ ቡድናችን በዛሬው ጨዋታ ሙሉ ቀይ መለያ ይለብሳል።
