0
Items : 0
Subtotal : 0.00Br
View CartCheck Out

ሀይደር ሽረፋ በይፋ ይቅርታ ጠየቀ

የክለባችን ተከላካይ አማካይ ተጫዋች የሆነው ሀይደር ሸረፋ በ14ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ ሜዳ ላይ ባሳየው ያልተገባ ባህሪ መላውን እግር ኳስ አፍቃሪ ህዝብ ይቅርታ ጠየቀ።
ተጫዋቹ ትናንት ከኢትዮጵያ ቡና ጋር በነበረው ጨዋታ ላይ ተቀይሮ ከገባ ከጥቂት ደቂቃዎች በኃላ ከቡናው ተጫዋች በተሰነዘረበት አስነዋሪ ስድብ ራሱን መቆጣጠር ባለመቻሉ ድርጊቱን በመፈፀሙ መላውን የስፖርት ቤተሰብ ከልቡ ይቅርታ ጠይቋል።
ሀይደር በእለቱ በመሀል ዳኛው ውሳኔ በቀይ ካርድ ከሜዳ መውጣቱ ይታወሳል ።

Leave a Reply

Our Shop

Cart